ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር በሚል መሪ ቃል የምርጫ ቅስቀሳና ቡና ጠጡ ፕሮግራም ተካሄደ
በካፋ ዞን ጠሎ ወረዳ ጉታ ቀበሌ በሴቶች ክንፍ አስተባባሪነት የምርጫ ቅስቀሳና ቡና ጠጡ ፕሮግራም ተካሂዷል።
በቡና ጠጡ ፕሮግራም ሴቶች በ7ተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲን እንዲመርጡ ግንዛቤ መስጠት ተችሏል።
በምርጫው የብልጽግና ፓርቲ ምልክት የስንዴ ነዶ በመሆኑ የስንዴ ነዶ እንዲመርጡ የተገጸ ሲሆን ፕሮግራሙ በሁሉም ቀበሌዎች እንደሚካሄድ ተጠቁሟል።
በፕሮግራሙ ላይ የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ ወ/ሮ አልማዝ ብርሃኑ፣ የሴቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ቅድስት አበበ እና በፈለገ-ሠላም ምርጫ ክልል የክልል ምክርቤት እጩ ተወካይ ወ/ሮ ሸዋይ አግደውን ጨምሮ የክንፉ አመራሮችና አባላት ተገኝተዋል።
#Prosperity