በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጌዴኦና ኮሬ ዞኖች ሴቶች ክንፍ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳና ሴት እጩዎችን የማስተዋወቅ መርሃ ግብር አካሄደ
የሴቶች ክንፍ አባላት የብልጽግና ፓርቲ ምልክትና የተለያዩ መፈክሮችን በማሰማት በቀጣይ በሚከናወኑ ሀገራዊ ተልዕኮዎች ላይ ሴቶች በንቃት እንደሚሳተፉና ለውጤታማነት የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልፀዋል።
"ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል ለሚካሄደው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍና የኮሬ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ በሰልፍና በተለያዩ ኩነቶች የታጀበ ደማቅ የቅስቀሳ ፕሮግራም አካሂደዋል።
#prosperity