በነፋስ መውጫ ከተማ ለብልፅግና ፓርቲ ደማቅ የድጋፍ ሰልፍ በመካሄድ ላይ ነው
በደቡብ ጎንደር ዞን የላይ ጋይንት ወረዳና የነፋስ መውጫ ከተማ አስተዳደር በጋራ በተዘጋጀ የብልፅግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ በመካሄድ ላይ ሲሆን ህዝቡ በነቂስ በመውጣት የለውጡን መንግስት እንደሚደግፍና እንደሚመርጥ በድጋፍ ሰልፍ አረጋግጧል።
በነፋስ መውጫና በላይ ጋይንት ወረዳ በዙሪያው በሚገኙ ቀበሌዎች ህዝቡ በነቂስ በመውጣት የለውጡን መንግስት በመደገፍ ለመምረጥ መዘጋጀቱን የተለያዩ መፈክሮችን በማሰማት ድጋፉን በመግለፅ ላይ ነው።
በህዝባዊ ንቅናቄ የምረጡኝ የቅስቀሳ ፕሮግራሙ ላይ አመራሮች ፣ በነፋስ መውጫና በዙሪያው የሚገኙ ነዋሪዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
#prosperity