ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት አስመልክቶ በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ በለውጡ ለተገኘው ድልና ስኬት እውቅና የሚሰጥ ታላቅ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ይገኛል
በድጋፍ ሰልፉ ወጣቶች፣ሴቶይ፣ የሐይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ሀደ ሲንቄዎችን ጨምሮ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
ሰልፈኞቹ በመልዕክቶቻቸው ከመጋቢት እስከ መጋቢት የተመዘገቡ የስኬት ጉዞዎችን በመግለጽ፤ በመጋቢት 24 ተምሳሌታዊ ጉዞ እና መሰረታዊ ርምጃ የተመዘገቡ ስኬቶችን አድንቀዋል።
በለውጡ መንግሥት እየተከናወኑ ያሉ የልማት ተግባራትን በመደገፍ፣ በቀጣይም የተሻለ ስራ እንዲሰራ ከመንግሥት ጋር በትብብር እንደሚሰሩ የሚያረጋግጡ መልዕክት እያስተላለፉ ይገኛል።