“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ
የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ በአምራች ኢንደስትሪው ዘርፍ የሚታዩ መዋቅራዊ ማነቆዎችን በመቅረፍ ረገድ የሚከተሉትን ተጨባጭ ውጤቶች አስመዝግቧል፦
የትስስርና የግብዓት አቅርቦት
ከፍተኛ የግብዓት ዕድገት ለማሳየቱ አብነቶቹ ብዙ ናቸው።
• አጠቃላይ የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ከ29 ሚሊዮን ቶን ወደ 76 ሚሊዮን ቶን አድጓል።
• ዓመታዊ አማካይ የግብዓት አቅርቦት ከ9 ሚሊዮን ወደ 15 ሚሊዮን ቶን ከፍ ያለ ውጤት አስመዝግቧል።
መሠረተ-ልማትና መሬት እንዲሁም የኃይል አቅርቦትን በተመለከተ፦
• ለኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የሚውል 3.4 ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ተመድቧል።
• የለማ መሬት ዝውውር በሰባት እጥፍ በማደግ በ2018 25,728 ሄክታር ደርሷል።