ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቅዱሱን የረመዳን ወር ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች የኢፍጣር መርሐ-ግብር አካሄዱ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ዓመታዊ ባህል” ሲሉ የገለጹትን የቅዱሱን የረመዳን ወር ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች የኢፍጣር መርሐ-ግብር አካሂደዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንኑ በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት፣ “የዛሬው ኢፍጣር በመተዛዘን፣ በፍቅር፣ በአንድነት እና ማኅበራዊ ዋጋን ከፍ በማድረግ ተከናውኗል” ብለዋል።