የአፍሪካ ጣሊያን ፎረምን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት
በመደመር መንፈስ ኢትዮጵያ ከጣሊያን ሪፐብሊክ መንግሥት ጋር በመተባበር ሁለተኛውን የጣሊያን-አፍሪካ ጉባዔ የካቲት 6፣ 2018 በአዲስ አበባ በማስተናገድ በጣሊያን እና በአፍሪካ መካከል ድልድይ ሆናለች፡፡ የሰው ዘር መገኛ እንደመሆናችን የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ግንኙነቶችን ለማጠናከር እንዲሁም በመላው አፍሪካ የንግድ፣ የፈጠራ እና የኢንቨስትመንት ሥራዎችን ለማሳደግ ለጋራ እድገት እንሰባሰባለን፡፡
የጉባዔው ተሳታፊ ልዑካንና እንግዶቻችን፣ የመነሻ መሰረታችን እና የነገ ዘላቂ አጋርነቶች ወደ ሚገነቡባት ሁለተኛ ቤታችሁ ወደሆነችው ኢትዮጵያ እንኳን ደህና መጣችሁ!