የፌዴራል ፖሊስ በመስቀል አደባባይ የተለያዩ ትርኢቶችን በማሳየት ላይ ነው
የፌዴራል ፖሊስ በዛሬው ዕለት በመስቀል አደባባይ የተለያዩ ትርኢቶችን በማሳየት ላይ ይገኛል፡፡ላለፉት ሁለት አመታት የፖሊስን ተቋም ለማዘመን የተለያዩ ስራዎች ሲከናወኑ እንደነበር የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
ይህንን የተመለከተ ሲምፖዚየም ከትናንትና ጀምሮ ሲደረግ እንደነበር ተገልጿል።ባለፉት ሁለት አመታት ህብረተሰቡንና ፖሊስን የበለጠ ማቀራረብ፣ በስነ ምግባር የታነፀ የፖሊስ ሰራዊትን ለመገንባት፣ የፖሊስ ሰራዊት ህብረተሰቡ የሚፈራው ሳይሆን የሚያከብረው እንዲሆን ከማድረግ አኳያ በርካታ ስራዎች ተሰርቷል ተብሏል።
በሀገራችን የፖሊስ ሰራዊት በ1934 ዓ.ም መመስረቱ የሚታወስ ነው።