You are currently viewing በመተከል ዞን በተከሰተው የፀጥታ ችግር ውስጥ እጃቸው ያለባቸውና በቸልተኝነት ኃላፊነት በአግባቡ ባልተወጡ ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ አመራሮች ላይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብልጽግና ፓርቲና በሚመራው መንግስት ህጋዊና ፖለቲካዊ እርምጃ ተወስዷል

በመተከል ዞን በተከሰተው የፀጥታ ችግር ውስጥ እጃቸው ያለባቸውና በቸልተኝነት ኃላፊነት በአግባቡ ባልተወጡ ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ አመራሮች ላይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብልጽግና ፓርቲና በሚመራው መንግስት ህጋዊና ፖለቲካዊ እርምጃ ተወስዷል

  • Post comments:0 Comments

በመተከል ዞን በተከሰተው የፀጥታ ችግር ውስጥ እጃቸው ያለባቸውና በቸልተኝነት ኃላፊነት በአግባቡ ባልተወጡ ከክልል እስከ ወረዳ ያሉ አመራሮች ላይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብልጽግና ፓርቲና በሚመራው መንግስት ህጋዊና ፖለቲካዊ እርምጃ ተወስዷል በዚሁ መሰረት:-

በክልል ደረጃ 1. አቶ አበራ ባየታ የሰላም ግንባታና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ በሽግሽግ ወደ ሌላ ቢሮ ተዛሯል

2. ኮማንደር ነጋ ጃራ ም/ል የፖሊስ ኮሚሽነር ከኃላፊነት ተነስቷል

3. ኮማንደር ወጋሪ ፖሊኖ የክልሉ ልዩ ኃይል አዛዥ ከኃላፊነት ተነስቷል

መተከል ዞን አመራሮች

1. አቶ ሻንበል ሌንጫ የጉሙዝ ብሄረሰብ ምክትል አፈ-ጉባኤ ከኃላፊነት ተነስቷል

2. አቶ አብደላ ኢብራሂም የጤና መምሪያ ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

3. አቶ አጥናፉ አቢዞ የንግድ መምሪያ ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

4. አቶ ለሜሳ ይርሳው ገንዘብና ኢኮኖሚ መምሪያ ኃላፊከኃላፊነት ተነስቷል

5. አቶ ሙሉአለም ማሞ የፍትህ መምሪያ ኃላፊከኃላፊነት ተነስቷል

6. ወ/ሮ ዞማ ቁንዴ መ/ኮ/ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

7. ወ/ሮ አልማዝ እምቢያለ ሴቶችና ህፃናት መምሪያ ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

8. አቶ ቴዎድሮስ ፈይሳ የግብርና መምሪያ ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

ቡለን ወረዳ

1. አቶ ነመራ ማሩ ቡለን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ከኃላፊነት ተነስቷል

2. አቶ ቢዲቃ ክዊ ቡለን ወረዳ ም/ዋና አስተዳዳሪ ከኃላፊነት ተነስቷል

3. አቶ በልፊ ሰንበታ ዋና አፈ-ጉባኤ ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

4. ወ/ሮ ስኳረ ተፈራ ምክትል አፈ ጉባዔ ከኃላፊነት ተነስቷል5. አቶ ብኩር ስዩም የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

ወምበራ ወረዳ

1. አቶ ሂካ አንበሳ ዋና አስተዳዳሪ ከኃላፊነት ተነስቷል

2. አቶ ምህረት አባተ ዋና አፈ ጉባኤ ከኃላፊነት ተነስቷል

3. አቶ አስቻለ ገሰሰ ጤና ጥበብ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል4. አቶ ቻለ ኡስማን ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

5. አቶ በላይ ኢብራሂም የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ፋይናንስ ዘርፍ ከኃላፊነት ተነስቷል

ዳንጉር ወረዳ

1. አቶ ደሳለኝ እንድሪያስ ዋና አስተዳዳሪ ከኃላፊነት ተነስቷል

2. አቶ ልጃለም ኃይሉ ም/ዋና አስተዳዳሪ ከኃላፊነት ተነስቷል

3. አቶ እያሱ ሻውል ዋና አፈ-ጉባኤ ከኃላፊነት ተነስቷል

4. አቶ ፓርሻዊ አስማ የፀጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

5. አቶ አለሙ ጃለታ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

6 አቶ በዛብህ ሂንጮ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

7. አቶ ምንችል ገፂ ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

8. አቶ ቸረ በላቸው የከተማ ስራ አስኪያጅ ከኃላፊነት ተነስቷል

9. አቶ ጀግናማው ማንጎ ሚኒሻ ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

ድባጢ ወረዳ

1. አቶ አንበሳ ወዲ ትምርህት ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

2. አቶ መንግሥቱ መለሰ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

3. አቶ አዝመራው ጌታቸው ቴክኒክና ሙያ ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

4. አቶ አበጀ ከበደ ም/ዋና አፈ ጉባኤ ከኃላፊነት ተነስቷል

5. አቶ ያደታ ጌታቸው ሚኒሻ ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

ማንዱራ ወረዳ

1. አቶ ማንጎ ሰንበታ ሚኒሻ ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

2. ወ/ሮ አብነት ክዊ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

3. አቶ አዲሱ ዳዳሀ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ባ/ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

4. አቶ ባሩድ አባያ ገንዘብና ኢኮኖሚ ጽ/ቤት ከኃላፊነት ተነስቷል

5. አቶ ጋንቺኳ ቲኳን ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

ጉባ ወረዳ

1. አቶ ባግድ ባልቻ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

2. አቶ ተካሳ ውሳ ም/ል ዋና አስተዳዳሪ ከኃላፊነት ተነስቷል

3. ዊሊያም ራሽድ መ/ኮ/ ባህል ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

4. አቶ መንግቱ ፖሊስ ገንዘብና ኢኮኖሚ ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

5. ቁሪስ ታየ ንግድ ጽ/ቤት ኃላፊ ከኃላፊነት ተነስቷል

45 አመራሮች ላይ እርምጃ ከተወሰዱት ውስጥ አንድ የአመራር ሽግሽግ የተደረገ ሲሆን ሌሎቹ በሙሉ ከኃላፊነት እንዲነሱ ተወስኗል። ከመካከላቸው 10ሩ አመራሮች በህግ እንዲጠየቁና ምርመራ እንዲጣራባቸው ተደርጓል።

በሌላ በኩል 1. አቶ ጋሹ ዱጋስ የፀጥታና ሰላም ግንባታ ቢሮ ኃላፊ

2. አቶ አበራ ባየታ የውሃ ቢሮ ኃላፊ

3. ኢ/ር ምስጋና ኢንጂፋታ የፓሊሊኮ/ምክትል ኮሚሽነር

4. አቶ ብርሀኑ አየሁ ዋና ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ

5. አማር ረጀብ ዋና ጠቅላይ አቃቤ ህግ አ/ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ሆነው ሽግሽግና አዲስ አመራር ምደባ ተሰጥቷል።

ምላሽ ይስጡ