You are currently viewing የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ የክተት አዋጁን ተቀብለው ወደ ጦር ግምባር መዝመታቸው ተገለፀ

የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ የክተት አዋጁን ተቀብለው ወደ ጦር ግምባር መዝመታቸው ተገለፀ

  • Post comments:0 Comments
የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ የክተት አዋጁን ተቀብለው ወደ ጦር ግምባር መዝመታቸው ተገለፀ
 
የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ግርማቸው አባተ የክተት አዋጁን ተቀብለው ወደ ጦር ግምባር ዘምተዋል፡፡
ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ግርማቸው አባተ ከአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚነት በተጨማሪ የኢንዱስትሪ ልማት ፅ/ቤት ኃላፊነትን ደርበው ሲሰሩ እንደነበር የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ያወጣው መረጃ ያመለክታል፡፡
 
መንግስት አውጆት የነበረውን የተናጠል የተኩስ አቁም ስምምነት ተከትሎ የህወሓት የሽብር ቡድን በአጎራባች ክልሎች ላይ ወረራ በመፈፀሙ ዜጎች አገራቸውን እንዲታደጉ በቀረበው ጥሪ መሰረት ተሳትፏቸውን በተለያየ መልኩ እየገለፁ ይገኛል፡፡
 
የተናጠል ተኩስ አቁሙ ትላንት መነሳቱን ተከትሎም ሁሉም ኢትዮጵያዊዊ የሽብር ቡድኑ በአገር ላይ የደቀነውን ስጋት ለመቀልበስ በሚደረገው ጥረት ተሳታፊ እንዲሆን ጥሪ መቅረቡ ይታወሳል፡፡

ምላሽ ይስጡ