የብርሸለቆ ውትድርና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የ34ኛ ዙር ምልምል ሰልጣኞች የመክፈቻ ስነ‐ስርዓት አካሄደ
የብርሸለቆ መሰረታዊ ውትድርና ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የ34ኛ ዙር ምልምል ሰልጣኞች የመክፈቻ ስነ‐ስርዓት አካሄደ።
የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ ዋና አዘዥ ኮሎኔል ጌታቸው አሊ ፣ ሀገራችሁን በቅንነት ለማገልገል የውትድርና ሙያ በመምረጥ በሀገራችን የሚቃጣውን ማንኛውንም ጥቃት ለመከላከል ፣ አሸባሪውን ቡድን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመደምሰስ፣ ህዝብና ሃገርን ለመጠበቅ ጀግንነት የተሞላበት ውሳኔ ወስናችሁ እንኳን የጀግኖች መፍለቂያ ወደ ሆነው ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት በሰላም መጣችሁ ብለዋል።