You are currently viewing የሰላም ጓድ አባላት ከኢትዮጵያ ህዝብና መንግሰት ጎን እንደሚቆሙ ገለጹ

የሰላም ጓድ አባላት ከኢትዮጵያ ህዝብና መንግሰት ጎን እንደሚቆሙ ገለጹ

  • Post comments:0 Comments
የሰላም ጓድ አባላት ከኢትዮጵያ ህዝብና መንግሰት ጎን እንደሚቆሙ ገለጹ
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በፕሮፌሰር ብሩክ ኃይሉ ከተመራው የሰላም ጓድ አባላት ጋር በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡
የሰላም ጓድ አባላት በአገራችን እየተሰሩ ባሉ ሥራዎች በመደሰታቸው ምስጋና ለማቅረብ እና አሁን በአገራችን ባሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከኢትዮጵያ መንግሰትና ህዝብ ጎን መቆማቸውን ለማረጋገጥ ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸውን የቡድኑ አስተባባሪ ፕሮፌሰር ብሩክ ገልጸዋል፡፡
በአሜሪካን አገር ከተለያዩ ማህበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ የቡድኑ አባላት በማሳተፍ በልማት ሥራዎች ፣በተራድኦ ተግባራት እና በአገር ገጽታ ግንባታ እያበረከቱ ያሉት የስራ እንቅስቃሴ ዙሪያ ለአቶ ደመቀ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
አቶ ደመቀ ቡድኑ እያደረገ ስላለው በጎ ተግባራት እና ከኢትዮጵያ ጎን በመቆማቸው ምስጋና አቅርበው፤ ሥራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል፡፡ በተያያዘም መንግስት የቡድኑን እንቅስቃሴ ለመደገፍ ፍላጎት እንዳለው አረጋግጠዋል ሲል የቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ዘግቧል።

ምላሽ ይስጡ