You are currently viewing ኢትዮጵያችን የዘመናት ፈታኞቿ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሸነፉና ብሩህ ተስፋዋ እየበዛላት በመሆኑ ሁላችንም እንደሰታለን። ለዚያ ደስታ ስለታጨን በእርግጥም ሀሴት ማድረግ ይገባናል፡፡

ኢትዮጵያችን የዘመናት ፈታኞቿ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሸነፉና ብሩህ ተስፋዋ እየበዛላት በመሆኑ ሁላችንም እንደሰታለን። ለዚያ ደስታ ስለታጨን በእርግጥም ሀሴት ማድረግ ይገባናል፡፡

  • Post comments:0 Comments

ነገር ግን ለታላቅ ደስታ የታጨ ሁሉ እስከመጨረሻው በጽናት ይጓዛል፤ ድልን ይጎናጸፋል ማለት አይደለም። በክርስቶስ የማዳን መንገድ የአዳም ዘር በሞላ ለደስታ ቢታጭም እንደ ይሁዳ ያሉት በመንገዱ ተሸንፈው ስለወደቁ የድሉ ባለቤት አልሆኑም።

ስለዚህ የተስፋ መንገዳችን በስኬት እንዲቋጭ ዛሬም ሆነ ነገ ፈተናውን በድል መወጣት ይኖርብናል። በየመንገዳችን የሚገጥሙን ፈተናዎች ወደ ተስፋ መሻገሪያ በሮቻችን ናቸው፡፡

ጥምቀቱና ስቅለቱ ለክርስቲያናዊው የቅድስና ጉዞ የመዳን በሮች እንደሆኑት ሁሉ እንደ ሀገር ለምናደርገው የዲሞክራሲ ጉዞ ከፊታችን የሚጠብቀን ምርጫ በድል ከተወጣነው አንዱ የተስፋ በራችን መሆኑ አይቀርም። ስለዚህ ሁላችንም ጥሩ ዝግጅት አድርገንና መንፈሳችንን አጽንተን በድል ልንሻገረው ይገባል፡፡

ምላሽ ይስጡ