You are currently viewing የአዲስ አበባ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ አመራር በከተማውና ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ ላይ ተወያይቶ የተለያዩ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል

የአዲስ አበባ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ አመራር በከተማውና ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ ላይ ተወያይቶ የተለያዩ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል

  • Post comments:0 Comments

ይህ አጥፊ ቡድን በከተማችን ላይ በተለያዩ አከባቢዎች ሁከትና ግርግር ለመፍጠር በተለያዩ ቦታዎች ላይ ቦንቦችን ከቆሻሻ ጋር አብሮ በመጣል ሰላማችንን ለማደፍረስ እየሰራ በመሆኑ ሁሉም የከተማችን ህብረተሰብ አከባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ እና የእነዚህ አጥፊ ሀይሎች ሴራ እንዲከሽፍ ሁሉም ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር በመሆን የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለበት ተገልጿል ።ጁንታው የህወሓት ቡድን ሀገርን ለማተራመስ ያሴረው ሴራ ጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊታችን በመመከት ላይ ይገኛል ።

ይህን የጥፋት ሀይል በከተማችን የሚገኙ የትግራይ ተወላጆችም ለሀገር ጸር የሆነውን አጥፊ ቡድን መንግስት የጀመረውን ህግን የማስከበር ዘመቻ ጎን እንዲሰለፉ እና ከሀገር መከላከያ ጎን እንዲቆሙ ጥሪ ቀርቧል ።አመራሩም በከተማዋ የሚገኙ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማስተባበር ለመከላከያ ሰራዊታችን የተጀመረው የድጋፍ ስራ አመርቂ ውጤቶች እየታዩ ሲሆን በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው ተገልጿል ።

ምላሽ ይስጡ