ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዋሽንግተን ዲሲ ከሚኖሩ የኢትዮጵያ ኮሙዩኒቲ አባላት ጋር ተወያዩ
በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ እየተካሄደ በሚገኘው የአሜሪካ-አፍሪካ ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙርያ ተወያይተዋል።
ከዚህ በፊት ዳያስፖራውን ጨምሮ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ያነሳቸው የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት መንግሥት ባለፉት አራት ዓመታት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የሕግ ሪፎርሞችን ማከናወኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ አሁን እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችንም በዘላቂነት ለመፍታት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው ብለዋል።
ዳያስፖራውም እያደረገ ያለውን ሀገሩን የማገዝ ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አሳስበዋል።