የምንደመረው ነገን በጋራ ለማነጽ፣ እንግዶቻችንን በፍቅር ለመቀበልና ለማስተናገድ፣ ደካማውን ለማገዝ፣ ያለንን ለማካፈል፣ ተግተን ለመስራት፣ የበደሉንን ይቅር ለማለት፣ በፍቅር ሁሉን ለማሸነፍ፣ የወደፊት ዕጣ ፈንታችን ከመበላላት መረዳዳት፤ ከመገፋፋት መተቃቀፍ እንዲሆንልን ነው።
• በመደመር ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን እንሰራለን። ሳንደመር ስንቀር ኪሳራው ብዙ ነው።
• መልካችን፣ ፍቅራችን፣ ደግነታችን፣ ጀግንነታችንም አንድ ዓይነት ነው። ነገር ግን የእኛ መደመር ለሌሎች አፍሪካ ወንድሞቻችን ስጋት ሳይሆን ተስፋ፤ ጦርነት ሳይሆን ልማት፤ የሚቀንስ ሳይሆን የሚጨምር ነው።
በአንድ ወቅት የፓርቲያችን ፕሬዝዳንት ስለ መደመር እሳቤ የተናገሩት።