You are currently viewing ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ካስተላለፉት መልዕክት በጥቂቱ፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ካስተላለፉት መልዕክት በጥቂቱ፡

  • Post comments:0 Comments

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ካስተላለፉት መልዕክት በጥቂቱ፡-

  • ጀግኖች የኢትዮጵያ ልጆች በመሬት ላይ ያስገኙትን ታሪካዊ ድል በደቡብ አፍሪካ በነበረው የሰላም ውይይት ዳግም የሚያስረግጥ የሰላም ድል ማግኘት ተችሏል፤
  • በድርድሩ ኢትዮጵያ ያቀረበችው ሃሳብ 100 በመቶ ተቀባይነት አግኝቷል፤
  • የዛሬ ሁለት ዓመት ባልተገባ መንገድ ከወንድሞቻችን እጅግ አሳዛኝ ጥቃት ተሰንዝሮብን ነበር፤ የኢትዮጵያ ልጆች በገዛ ወንድሞቻቸው ባልተገባ ሁኔታ በተኙበት ታርደው፣ ተገድለው፣ ተገፍተው ነበር፤
  • በኢትዮጵያ ሉአላዊነት እና አንድነት ለመጣ ሁሉ ግንባራችንን ለአረር ለመስጠት ዝግጁ መሆናችንን ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ያሳየንበት ነበር፤
  • ኢትዮጵያ የምትፈልገው ሰላምና ብልፅግና እንጂ ጦርነት አይደለም፤
  • በደቡብ አፍሪካ በነበረው የሰላም ድርድር ጀግኖች የኢትዮጵያ ልጆች በመሬት ላይ ያስገኙትን ታሪካዊ ድል ዳግም የሚያስረግጥ የሰላም ድል ማግኘት ተችሏል፤
  • ከተገኙ ዋና ዋና ድሎች መካከል አንደኛው የኢትዮጵያ ሉአላዊነትና የግዛት አንድነት ለድርድር አይቀርብም፤
  • ለኢትዮጵያ አንድነት የሞቱና የቆሰሉ ጀግኖች ራዕያቸውና ህልማቸው ዕውን ሆኗል፤
  • በአንድ አገር መኖር ስለሚገባው የአገር መከላከያ ሠራዊት አስፈላጊነት ላይ መግባባት ላይ ተደርሷል፤
  • እንደ ጋሞ ባሉ አባቶች እግር ሥር ያደገ ሁሉ ነገር በንግግርና በውይይት እንደሚፈታ ያውቃል፤
  • በአንድ አገር ውስጥ ከአንድ መከላከያ በላይ አያስፈልግም በሚለው ጉዳይ ከስምምነት ላይ ተደርሷል
  • ሕጋዊነትን ማስፈን ላይ በተደረገው ውይይትም ሕግ መከበር ይኖርበታል፤

#prosperity

Leave a Reply