በመጪው ዘመን ብዝሃነታችንን በጌጥነት ተቀብለን መታረቅ የሚችል ሀሳባችንን አስታርቀን መከበር የሚገባው ልዩነቶቻችንን አክብረን ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን አጠንክረን ወደ ከፍታ የምንተምበት ጊዜ ይሆናል፡፡ይህም እንዲሳካ የፖለቲካ ልዩነቶቻችንን ለማጥበብ አካታች ብሔራዊ የውይይት መድረክ እናካሂዳለን፡፡
የምክክር ሂደቱ ችግሮቻችንን በጠረንጴዛ ዙሪያ ይፈታሉ ብለው የሚያምኑትን የሚያካትት በፖለቲካ ልሂቃን መካከል የሚደረግ ብቻ ሳይሆን ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፎን ያገናዘበ አጠቃላይ ሂደቱ አካታችና አሳታፊ እንዲሁም በኢትዮጵያዊያን እየተመራ አገር በቀል መፍትሔዎች ለማፍለቅ ታልሞ የሚከናወን ይሆናል፡፡
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ