ብልፅግና ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የ14 አቅመ ደካማ እናቶችን ቤት ሊገነባ ነው
የክረምት በጎ ፍቃድ አካል የሆነው የአቅማ ደካሞችን ቤት የማደስ ሰራ በክረምቱ መግቢያ ላይ በፓርቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አብይ አህመድ አስጀማሪነት ይፋ መደረጉ ይታወቃል።
ባለፉት የክረምት ወራትም የተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት እንዲሁም በባለሃብቶች በሺዎች የሚቆጠሩ አቅመ ደካሞች ቤት ማደሳቸው ይታወቃል።
የብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሲኖሩ የነበሩ 14 አቅመ ደካማ እናቶችን ቤት የማደስ ስራ ዛሬ አስጀምሯል።
ቤቶቹ ከፍ ባለ ጥራት ደረጃቸውን ጠብቀው እንዲገነቡ ሲባል እንዲሁም ዜጎች በምቹ ሁኔታ ውስጥ እንዲኖሩ ማድረግ የፓርቲው ዋና አላማ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ ለቤት ግንባታ ፕሮጀክቱ በጀት ተመድቧል።