ብልጽግና ፓርቲ ለስድስተኛው ሃገራዊና ክልላዊ ምርጫ “ሕብረ ብሔራዊነት ለጋራ ብልጽግና” የሚል መሪ ቃል ሲኖረው የምርጫ ምልክት ያደረገው ደግሞ የሚበራ አምፖልን ነው፡፡ምርጫው ከምንጊዜው በላይ ሰላማዊ፣ዴሞክራሲያዊና በህዝብም ዘንድ ፍጹም ተዓማኒ እንዲሆን ብልጽግና ፓርቲ እየሰራ ይገኛል፡፡
ከውስጥም ከውጭም የሚፈጠሩ ጫናዎችን ተቋቁሞ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊያን አድማሷ በብልጽግና ይሸፈን ዘንድ የሚታትረውን ብልጽግና ፓርቲ በመምረጥ የውድ ሃገርዎን የነገ ዕጣ ፋንታ በድምጽዎ ይወስኑ፡፡ የህዝብና የሃገር ክብር ከምንም በላይ ነው፡፡
ብልጽግና ፓርቲን ይምረጡ