You are currently viewing የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ዑመር ህዝበ ሙስሊሙ የኢድ አል ፈጥርን በዓል በሰላምና በአንድነት እንዲያከብር ጥሪ አስተላለፉ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ዑመር ህዝበ ሙስሊሙ የኢድ አል ፈጥርን በዓል በሰላምና በአንድነት እንዲያከብር ጥሪ አስተላለፉ

  • Post comments:0 Comments
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ዑመር ህዝበ ሙስሊሙ የኢድ አል ፈጥርን በዓል በሰላምና በአንድነት እንዲያከብር ጥሪ አስተላለፉ
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ዑመር እድሪስ 1442ኛውን የኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላምና በአንድነት እንዲያከብሩ ለህዝበ ሙስሊሙ ጥሪ አቅርበዋል።
በዓሉንም ከሌላቸው ማህበረሰብ ጋር በጋራ ማክበር እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት።
በዛሬው ዕለትም የኢፍጣር ስነ ስርዓት በጎዳና ላይ እንዲደረግ ከአዲስ አበባ ከተማ ፈቃድ መገኘቱንም ገልጸዋል።
ህዝበ ሙስሊሙ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ያለው ሰላም እንዲጠበቅ ለፈጣሪ ዱአ እንዲያደርግና አንድነቱንና ልማቱን እንዲያጠናክርም ነው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ዑመር እድሪስ የገለፁት።
ዛሬ ማታ ጨረቃ ከታየች በዓሉ ነገ ረቡዕ የሚከበር ሲሆን፣ ዛሬ ማታ ካልታየች ግን በዓሉ ሐሙስ እንደሚሆን ነው ሀጂ ሙፍቲ በመግለጫቸው ያስታወቁት።

ምላሽ ይስጡ