ሀገራዊ ሁለንተናዊ አላማዎቻችን እንዲሳኩ የተገኙ ድሎችን ጠበቆ በማስፋትና የተሠሩ ስህተቶችን በማረም ለመጪዉ ትዉልድ ጥቅም የሚተጋ የህዝቦች የልማት፤የዴሞክራሲ፤የነፃነትና የእኩልነት ፍላጎት በዘላቂነት የተሟላበት፤ በወንድማማችነት ላይ የተመሰረተ ህብረ-በሄራዊ አንድነትና የማይቆራረጥ ሰላም እዉን የሆነበት ኢትዮጵያን ለመገንባት ብልጽግና ፓርቲ ከመቼውም ጊዜ በላይ በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡
በአገራችን በተለይ ባለፉት ሶስት የለውጥ ዓመታት በሁሉም ዜጎች የጋራ ተሳትፎ እና እኩልነት ላይ የተመሰረተ ዘላቂ ሰላም መገለጫው የሆነ በመደመር እሳቤ የተቃኘ እና የኢኮኖሚ የማህበራዊና ፖለቲካዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ የቆዬ ሲሆን ጎን ለጎንም ይህንን ሂደት ሊያስተጓጉሉ የሚችሉ የጎታችና ሴረኛ መሰናክሎችን የመበጣጠስና ሃገራዊ ለውጡ በሙሉ አቅሙ በመደመር መንገድ ወደ ብልጽግና እንዲጓዝ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል፡፡
ብልጽግና ፓርቲ እንደ ሀገር የገጠሙትን ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ከመላው ኢትዮጵያዊያን ጋር ሆኖ ድል በመንሳት ወደ ብልጽግና የሚያደርገውን ጉዞ አጠናክሮ ይቀጥላል፤ምክንያቱም ከህዝብ ጋር ሆኖ የማይፈታ ችግር የለምና፡፡
ብልጽግናን ይምረጡ